በረኀብ 111 ሰዎች እንደሞቱ የተገለጸበት የአፅቢ ወረዳ ነዋሪዎች አስቸኳይ ርዳታ እንዲደርስላቸው ተማፀኑ

Your browser doesn’t support HTML5

በረኀብ 111 ሰዎች እንደሞቱ የተገለጸበት የአፅቢ ወረዳ ነዋሪዎች አስቸኳይ ርዳታ እንዲደርስላቸው ተማፀኑ

በትግራይ ምሥራቃዊ ዞን ኣፅቢ ወረዳ፣ ባለፉት ሦስት ወራት፣ 111 ሰዎች በረኀብ እንደሞቱ፣ የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የወረዳው የኢኮኖሚ ዘርፍ ሓላፊ አቶ ብርሃነ ገብረ፣ ባለፈው ክረምት፣ በወረዳው በቂ ዝናም ባለመዝነሙ ድርቅ እንደተከሠተ ጠቅሰው፣ በዚኽም፣ ከ82 ሺሕ በላይ ሕዝብ ለረኀብ እንደተጋለጠ ገልጸዋል፡፡

አኹን በወረዳው የተገኘው ምርት፣ ሕዝቡን ለመቀለብ የሚችለው ለ11 ቀናት ብቻ ነው፤ ያሉት ሓላፊው፣ የረኀብ አደጋው ለብዙዎች ሕይወት አስጊ እንደኾነ አመልክተዋል፡፡

የወረዳዋ ነዋሪዎችም፣ “ሞታችንን በዳጃችን ኾነን እየጠበቅን ነን፤” ሲሉ ረጂ አካላት አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርሷቸው ተማፅነዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።