የትግራይ ክልላዊ መንግሥት መግለጫ በወቅታዊ ጉዳይ

መቀሌ

የፌዴራሉ መንግሥት ለትግራይ አርሶ አደሮች የሴፍቲኔት ወይም የምግብ ለሥራ ፕሮግራም በጀት የሚውል 285 ሚሊዮን ብር ከለከለ ሲል የትግራይ ክልላዊ መንግሥት አስታውቋል።

የትግራይ ክልላዊ መንግሥት በዚህ የበጀት ጉዳይ እና በሌሎችም ጉዳዮች የፌዴራል መንግሥቱን የሚወነጅል መግለጫ አውጥቷል።

የፌዴራሉ የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ ትናንት በሰጠው መግለጫ በፌደሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ መሰረት ለክልሉ መንግሥት በቀጥታ የሚስጥ ምንም ዓይነት የበጀት ድጋፍ አይኖርም ብሏል።

የድጎማ በጀቱ ለትግራይ ወረዳዎች፣ ከተማዎችና ቀበሌዎች የሚሰጥበትን አሠራር ማዘጋጀቱም ገልጿል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ክልላዊ መንግሥት መግለጫ በወቅታዊ ጉዳይ