የትግራይ ክልል የመራጮች ምዝገባ ተጠናቀቀ

መቀሌ

ከሁለት ነጥብ ስድስት ሚልዮን በላይ መራጮች ለመመዝገብ ታቅዶ ከሁለት ነጥብ ሰባት ሚልዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸው የተነገረበት ትግራይ ክልል ውስጥ ይካሄዳል ለተባለው ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ትናንት ተጠናቋል።

የምርጫው ዝግጅት እየተካሄደ ያለው ኮሮናቫይረስን ለመከላከል ከሚደረግ ጥንቃቄ ጋር መሆኑንም ክልሉ ያቋቋመው የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።

በአንድ አንድ የክልሉ አካባቢዎች ምዝገባው በግዳጅ ሲካሄደ እንደነበረ የቀረቡ ስሞታዎችን አስመልክቶም “ተግድጃለሁ” ብሎ በክልሉ ውስጥ ያመለከተ እንደሌለ ኮሚሽኑ አመልክቷል።

የኮሚሽኑን አመራር አባል ተባባሪ ፕሮፌሰር መረሳ ፀሃዬን አነጋግረናል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ክልል የመራጮች ምዝገባ ተጠናቀቀ