“አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ” ክልል አቀፍ ኮሚቴ ሀብት የማሰባሰብ ንቅናቄውን በይፋ ጀመረ

Your browser doesn’t support HTML5

“አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ” ክልል አቀፍ ኮሚቴ ሀብት የማሰባሰብ ንቅናቄውን በይፋ ጀመረ

በትግራይ ክልል ያጋጠመውን ረኀብ ለመከላከል እንዲያግዝ የተቋቋመው ክልላዊ ኮሚቴ፣ ሀብት የማሰባሰብ ሥራውን በይፋ ጀመረ፡፡

ሀብት የማሰባሰቡ ንቅናቄ፣ “አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ” በሚል መሪ ቃል፣ ዛሬ ተጀምሯል፡፡

በሌላ በኩል፣ ዓረና ለዴሞክራሲ እና ለሉዓላዊነት ፓርቲ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እና ህወሓት፣ ለረኀቡ ትኩረት ከመስጠት ይልቅ በሥልጣን ሽኩቻ ተጠምደዋል፤ ሲል ወቀሷል፡፡

በክልሉ ለረኀቡ ተጎጂዎች ርዳታ ለመስጠት በሚደረገው ምዝገባም፣ በችግር ላይ የሚገኙ የፓርቲው አባላት እንደተከለከሉ፣ ፓርቲው አመልክቷል፡፡

የተረጂዎች ልየታው በርዳታ ሰጪ ተቋማት እንደሚከናወን የገለጸው፣ የክልሉ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ደግሞ፣ ፖለቲካን መሠረት ያደረገ የርዳታ አሰጣጥ ሥርዐት እንደሌለ ገልጾ የዓረናን ክስ አስተባብሏል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።