በሞቅዲሾ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 3 የፖሊስ መኮንኖች ተገድለዋል

Your browser doesn’t support HTML5

ሶማልያ ዋና ከተማ ሞቅዲሾ ውስጥ በሚገኝ አንድ የፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ ዛሬ ረቡዕ በደረሰ የመኪና ውስጥ ቦምብ ፍንዳታ፣ ቢያንስ 3 የፖሊስ መኮንኖች መገደላቸው ተሰማ።   የሞቅዲሾ ፖሊስ ዋና ኮሚሽነር አሊ ሀርሲ ባሬ እንደገለጹት፣ በፍንዳታው ክፉኛ የቆሰለው አሽከርካሪ ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር ውሏልኝ።   ፖሊስ ምርመራ እያካሄደ መሆኑንም ባሬ ጠቅሰዋል።