ሶርያ ውስጥ ከእስላማዊ መንግሥት ቡድን ሰዎችን ማውጣት ቀጥሏል

ፎቶ ፋይል

ሶሪያ ውስጥ ከመጨረሻው የእስላማዊ መንግሥት ቡድን ይዞታ ወንዶች፣ ሴቶችና ህፃናትን የማውጣቱ እንቅስቃሴ ቀጥሏል።

ሲቪሎቹ በበርካታ የጭነት መኪናዎች እያተጓጓዙ ሲሆን የህብረቱ ኃይሎች አውሮፕላኖች፣ ድሮኖች እና የተኩስ ድምፆች በተለያየ የበራሃው አካባቢ ተሰምተዋል።

በኋለኛው የሲቪሎች ማስወጣት እንቅስቃሴ ከስምንት መቶ እስከአንድ ሺህ የሚደርሱ ሰዎችን ለማውጣት እንደተቻለ ተዘግቧል፡፡