ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የሱዳንን የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋገሩ

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የሱዳን ከፍተኛ ምክር-ቤት ምክትል ሊቀ-መንበር የተመራ የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋገሩ

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሱዳን ከፍተኛ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር የተመራ የልዑካን ቡድንን ህዳር 21 በአስመራ ቤተመንግሥት ተቀብለው እንዳነጋገሩ የኤርትራ ማስታወቅያ ሚኒስቴር የመረጃ መረብ ሻባይት በድረ ገጹ ገልጿል።

በግንኙነቱ ወቅት፡ በሱዳን የሰላም ዋስትና ጥያቄ ላይ እንዲሁም በሱዳን መንግሥትና የትጥቅ ትግል ሲያካሂዱ በነበሩ ቡድኖች መካከል እየተካሄደ ስላለው የሰላም ግንኙነትን በተመለክተ በመወያየት በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረውን አዎንታዊ ግንኙነት ለማጠናከር በጋራ ለመስራት ኢንደተስማሙ ሻባይት ገልጿል።


የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የሱዳንን የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋገሩ