ካሜሩን ውስጥ አንድ ትምህርት ቤት 78 ተማሪዎች ተጠለፉ

  • ቪኦኤ ዜና
ሰሜናዊ ምዕራብ ካሜሩን ውስጥ ከሚገኝ አንድ የፕሪስቢቴሪያን ትምህርት ቤት፣ ማንነታቸው የማይታወቅ ታጣቂዎች ዳይሬክተሩን ጨምሮ 78 ተማሪዎችን መጥለፋቸው ተገለፀ።

ሰሜናዊ ምዕራብ ካሜሩን ውስጥ ከሚገኝ አንድ የፕሪስቢቴሪያን ትምህርት ቤት፣ ማንነታቸው የማይታወቅ ታጣቂዎች፣ ዳይሬክተሩን ጨምሮ 78 ተማሪዎችን መጥለፋቸው ተገለፀ።

ጠለፋው የተፈጸመው እንግሊዝኛ ተናጋሪ የሆነው አካባቢ ዋና ከተማ ባመነዳ ውስጥ ከሚገኝ ኝክወኢን መንደር መሆኑን፣ አስተዳዳሪው ዴበን ተቸሆፎ አረጋግጠዋል። የጠለፋው ምክንያትም ሆነ የጠላፊዎቹ ማንነት ገና አልታወቀም።