በፓሪስ ኦሊምፒክ የተመዘገበው ውጤት የዐዲስ አበባ ነዋሪዎችን አስከፍቷል

Your browser doesn’t support HTML5

በፓሪስ ኦሊምፒክ የተመዘገበው ውጤት የዐዲስ አበባ ነዋሪዎችን አስከፍቷል

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን፣ በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ያስመዘገበው ውጤት እንዳላስደሰታቸው፣ አስተያየታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የሰጡ የዐዲስ አበባ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡

ውጤቱ “ከለመድነውና ከጠበቅነው በታች ነው” የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ ለውጤቱ መውደቅ ምክንያት ነው ብለው የገመቱትንም አንሥተዋል፡፡ ችግሩ በጊዜ ካልታረመ የውጤት ማሽቆልቆሉ ተባብሶ ሊቀጥል እንደሚችልም ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡