ደቡብ ሱዳን በድንበር ጉዳይ ኬንያን ወነጀለች

  • ቆንጂት ታየ

Your browser doesn’t support HTML5

ደቡብ ጉዳን በድንበር ጉዳይ ኬንያን ወነጀለች

በአጨቃጫቂው ድንበር አካባቢ በማኅበረሰቦች መካከል በተካሄደ ግጭት ቢያንስ ስምንት ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ “ግዛቴን ልትወስድ ሞክራለች” ስትል ደቡብ ሱዳን ኬንያን ወነጀለች፡፡

የደቡብ ሱዳን መንግሥት የኬንያን አምባሳደር ጠርቶ ስሞታውን አቅርቧል፡፡ አጨቃጫቂውን የድንበር አካባቢ ደቡብ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ እና ኬንያ “ግዛቴ ነው” እያሉ ሲሆን ኬኒያ በድንበሩ በራሱ አካባቢ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2012 ዓ.ም የነዳጅ ሀብት አግኝታለች፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።