በሶማልያ አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ጥቃት አሥራ አራት ሰዎች ተገደሉ

  • ቪኦኤ ዜና
የሶማልያ ባለሥልጣኖች እንደሚሉት አንድ አጥፍቶ ጠፊ በታችኛው ሸበሌ ክልል በሚገኝ ገበያ ላይ ባደረሰው ጥቃት ቢያንስ አሥራ አራት ሰዎች ተገድለው 15 ቆስለዋል። ክልሉ ከሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ 90 ኪሎሜትር ርቆ ይገኛል።

የሶማልያ ባለሥልጣኖች እንደሚሉት አንድ አጥፍቶ ጠፊ በታችኛው ሸበሌ ክልል በሚገኝ ገበያ ላይ ባደረሰው ጥቃት ቢያንስ አሥራ አራት ሰዎች ተገድለው 15 ቆስለዋል። ክልሉ ከሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ 90 ኪሎሜትር ርቆ ይገኛል።

በፀጥታ ጉዳይ የክልሉ ምክትል አስተዳዳሪ አብዲፋታሕ ሐጂ አብዱሌ አጥፍቶ ጠፊው ዒላማ ያደረገው ሰው የሚበዛበትን የጫት ገበያን ነው ብለዋል።