የሲአን የባለቤትነት ጥያቄ

በከባድ የሥነ-ምግባር ግድፈት ከአመራር አባልነትና ከድርጅቱ የተሰናበቱ ግለሰቦች የሲዳማን ህዝብ ጥያቄ ለማደናቀፍ እየተንቀሳቀሱ ነው ሲል በአቶ ዱካሌ ላሚሶ የሚመራው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ /ሲአን/ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ከስሷል።

በሌላ በኩል "ህጋዊ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፤ ሲአን በኛ የሚመራ ነው" የሚለው የነ ዶ/ር ሚሊዮን ቱማቶ ቡድን "የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያለን እኛ ነን" ቢልም ባለው ሁኔታ ለማንም እውቅና እንደማይስጥ ነገር ግን በ2010 ዓ.ም. በተካሄደ በነ ዱካሌ ላሚሶ ምርጫ ላይ አቤቱታ ቀርቦ እየታየ መሆኑን ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ አሁን ገልጿል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሲአን የባለቤትነት ጥያቄ