በደቡብ ክልል፥ በጋሞ ጋፋ ዞን፥ የደምባ ጎፋ ወረዳ የሱካና የጉራደ ቀበሌ የሚኖሩ 38 አርሶ አደሮች በመንገድ ሥራ ምክንያት ከመሬታቸው መፈናቀላቸው፣የእርሻ መሬታቸው ከነ እርሻ ሰብሉ መውደሙን፣ መሬቱ ላይ አሸዋና ጠጠር ተቆልሎ ከዚህ በኋላ ማረስ እንዳልቻሉ፣ ልጆቻቸውን ማስተማርና ቤተሰቦቻቸውን መመገብ እንደተሳናቸው ገለጹ። ይህንን አቤቱታ ለአራት ዓመታት ለሚመለከተው አካል ቢያቀርቡም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኙ ገልፀው ከሥራቸው ተፈናቅለው ለጎዳና ሊዳረጉ መሆኑን ተናግረዋል።
Your browser doesn’t support HTML5
ከፌደራል መንገዶች ባለሥልጣንና የተጠቀሰው አቤቱታ እንደቀረበለትና አጥኒ ቡድን ልኮ ጉዳቱ ትክክለኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ ገልፆ በቀጣይ ካሳ እንደሚከፈል አስታውቋል።
አርሶ አደሮቹ በበኩላቸው እንዲህ ዓይነት ምላሽ ከዚህ ቀደም ማግኘታቸውን ነገር ግን በወረዳውም ሆኑ በክልሉ በኩል ምንም የተደረገላቸው ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
ጽዮን ግርማ ዝርዝር አላት።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ይከታተሉ።
Your browser doesn’t support HTML5