የሲዳማ አርነት ንቅናቄ የ/ሲአን/ መግለጫ

ሲአን

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ሂደት “ለመቀልበስ የሚደረጉ” ያላቸውን እንቅስቃሴዎች እንደሚቃወም የሲዳማ አርነት ንቅናቄ - ሲአን አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ሂደት “ለመቀልበስ የሚደረጉ” ያላቸውን እንቅስቃሴዎች እንደሚቃወም የሲዳማ አርነት ንቅናቄ - ሲአን አስታውቋል፡፡

ለውጡን “ከፍተኛ መስዋዕትነት የተከፈለበት” ብሎታል ሲአን። የተለያየ ስብጥር ባላቸው የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች መካከል “አለመተማመን እንዲኖርና ሁከት እንዲፈጠር የሚያደርጉ ኃይሎችን አወግዛለሁ" ብሏል ሲአን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ።

“በሃሳብ ልዕልናና በሰላማዊ መንገድ እንጂ ሁከት በመፍጠርና ሰላም በመንሳት የሚደረግ ትግል ተቀባይነት የለውም” ብሏል ንቅናቄው።

"የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ ነው" ያለው የሲዳማ ክልልነት ጥያቄ ውሣኔ-ሕዝብ ሂደት የደረሰበትን ደረጃ መንግሥት ለህዝብ እንዲያሳውቅ ሲአን ጠይቋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ የ/ሲአን/ መግለጫ