የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ በሰደድ እሳት በድጋሚ እየተቃጠለ ነው

የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ በሰደድ እሳት በድጋሚ እየተቃጠለ ነው

በተባበሩት መንግስታት የትምሕርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋም በቅርስነት በተመዘገበው የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ በሰደድ እሳት በድጋሚ እየተቃጠለ ነው።

የፓርኩ የማኅበረሰብና ቱሪዝም ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ታደሰ ይግዛው ፤ እሳቱን በምን እንደተነሳ ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ገልፀው፤ “ንፋስና ሙቀት ሲነካው እየተባባሰ ከፍተኛ ጉዳት እያስከተለ ነው” ብለዋል።

የ50 ዓመታት ዕድሜ ያለው እና የጎብኝዎች የዐይን ማረፊያ የሆኑ ብርቅዬ የዱር አራዊት እና እጽዋት መናኸሪያ በሆነው በዚህ ስፍራ ከጠቂት ቀናት በፊት የተነሳው የሰደድ እሳት ከ300 ሄክታር በላይ ደን መቃጠሉ ይታወሳል።

Your browser doesn’t support HTML5

የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ በሰደድ እሳት በድጋሚ እየተቃጠለ ነው