አል-በሺር ሳዑዲ አረቢያ ለሚካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ተጋብዘዋል

  • ቪኦኤ ዜና

ፎቶ ፋይል፡- የሱዳን ፕሬዚዳንት ሃሰን ኦማር አል በሺር

የሱዳን ፕሬዚዳንት ሃሰን ኦማር አል በሺር በያዝነው ሣምንት መጨረሻ ላይ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በሚካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸው የመብቶች ተሟጋቾችና ተንታኞችን እያነጋገረ ነው፡፡

የሱዳን ፕሬዚዳንት ሃሰን ኦማር አል በሺር በያዝነው ሣምንት መጨረሻ ላይ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በሚካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸው የመብቶች ተሟጋቾችና ተንታኞችን እያነጋገረ ነው፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በዚያ ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ይጠበቃል፡፡

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት በዓለምአቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በጦር ወንጀሎች ተከስሰው የሚፈለጉ በመሆናቸው መጋበዛቸው ንግግርና ውዝግብ ፈጥሯል፤ ተቃውሞም ገጥሞታል፡፡

ጂል ክሬግ ከናይሮቢ የላከችውን ዘገባ ትዝታ በላቸው ታቀርበዋለች፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

አል-በሺር ሳዑዲ አረቢያ ለሚካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ተጋብዘዋል