ውጥረት በዩክሬን

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ አውጭ የምክር ቤት አባላት የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዛሬ ሐሙስ ማለዳ ላይ በዩክሬን ላይ ያደረጉትን ወረራ አውግዘው የባይደን አስተዳደር ፈጣን እርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል፡፡ የአውሮፓ ኅብረትም ጠንካራ ማዕቀብ መጣሉን አስታውቋል፡፡

ሩሲያ በዛሬው ዕለት በዩክሬን ላይ ጥቃት ያደረሰች ሲሆን ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሌሎች ሀገራት ጣልቃ እንዳይገቡ አስጠንቅቀዋል፡፡