በኬንያ የባህር ዳርቻ በሃገር ማስጎብኘት ሥራ የተሰማሩ ሰዎች፥ ዩናይትድ ስቴትስ ባብዛኛው የጠረፉ አካባቢዎች ላይ ጥላ የቆየችውን የጉዞ እገዳ ለማንሳት የደረሰችበት ውሳኔ አስደስቷቸዋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
የጉዞ እገዳው፥ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሠራተኞች ጠረፉን እንዳይጎበኙ ይከለክላል፥ በተመሳሳይ የሃገር ጎብኚዎችም ወደ አካባቢው እንዳይሄዱ ይመክራል።
በኬንያ ናይሮቢ የዩናይትድ ስቴትስ የፕሬስ አታሼ ቲፋኒ መግርፍ (Tiffany McGriff) እገዳው የተነሳበት ምክንያት ”የኬንያ መንግሥት በወሰዳቸው አዎንታዊ እርጃዎች ቀድሞ ለእገዳው መደረግ ምክንያት የነበሩ ችግሮች ባሁኑ ጊዜ ስለሌሉ ነው” ብለዋል።
ያሜሪካ ድምፁ ጂል ክሬግ (Jill Craig) ከናይሮቢ ዘግቦበታል። ሰሎሞን ክፍሌ ያቀርበዋል። ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
ዋሺንግተን በኬንያ የጉዞ እገዳዋን አነሳች /ርዝመት -4ደ34ሰ/