የሱዳኑ ጦርነት፣ የትግራይ ተወላጆች ወደተጠለሉባቸው መጠለያ ጣቢያዎች እየተቃረበ መኾኑን በመጥቀስ፣ በዚያ ያሉትን ስደተኞች እንዲታደግ የተጠየቀው የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሠራ መኾኑን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት የስደተኞቹን ሕይወት እንዲታደግ፣ ትላንት ረቡዕ፣ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ ጥሪ ያቀረቡት፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የፌደራሉ መንግሥት የስደተኞቹ ሥቃይ እንዲያበቃ የሚችለውን ኹሉ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
It’s very unfortunate that the civil war and carnage in Sudan have continued unabated. The suffering of civilians is quite unimaginable. The situation has been further deteriorating very recently. As a home to tens of thousands of refugees from Tigray and also of other parts of…
— Getachew K Reda (@reda_getachew) July 3, 2024
በሱዳኑ ጦርነት መስፋፋት ችግር ላይ መውደቃቸውን የገለጹት ስደተኞቹም፣ የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርሱላቸው ተማፅነዋል፡፡
ስለ ጉዳዩ የአሜሪካ ድምፅ የጠየቃቸው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ የሱዳኑ ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ፣ መንግሥት ዜጎችን የማስመለስ ሥራ እያከናወነ መኾኑን ተናግረዋል፡፡
Your browser doesn’t support HTML5