የማሊኖውስኪ ኢንተርቪው ከቪኦኤ ጋር - ክፍል ሁለት

  • መለስካቸው አምሃ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የዴሞክራሲ የሠብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ

ለለውጥ የተገባውን ቃል ተግባራዊ ማድረግ የኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ሃላፊነት እንደሆነ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የዴሞክራሲ የሠብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ አሳሰቡ፡፡

ለተዛባ ዜና እና ለጥላቻ ንግግር መድሃኒቱ በርን መዝጋት ሳይሆን በሃገር ውስጥ ነፃ፣ ተቀባይነትን ላገኘና ሕያው ለሆነ መገናኛ ብዙሃን በርን በሠፊው መክፈት እንደሆነም ጠቆሙ፡፡

በኢትዮጵያ እንዲመጣ የሚፈለገው ለውጥ ሥርዓቱን ለዝነተ ዓለም ለማፅናት በሚደረግ ትግል ወይንም ሥርዓቱን በሃይል ለማፍረስ በሚወሰድ እርምጃም ሊሆን እንደማይችል አመለከቱ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣን ይህን የገለፁት ለቪኦኤ ብቻ በሰጡት ቃለ ምልልስ ሲሆን በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከመንግሥት ባለሥልጣናት ከፖለቲካ ተቃዋሚ መሪዎችና ከሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች ጋር መወያየታቸው ይታወቃል፡፡

በአዲስ አበባ ቆይታቸው ስላከናዎኗቸው ተግባራትና በተለያዩ ርዕሶች ላይ መለስካቸው አምሃ አነጋግሯቸዋል፣ የመጨረሻውንና ክፍል ሁለትን እንሆ፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

የማሊኖውስኪ ኢንተርቪው ከቪኦኤ ጋር - ክፍል ሁለት