ባይደን የኳድ መሪዎችን ስብሰባ በመኖሪያ ቤታችው ያስተናግዳሉ

  • ቪኦኤ ዜና

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን

Your browser doesn’t support HTML5

ባይደን የኳድ መሪዎችን ስብሰባ በመኖሪያ ቤታችው ያስተናግዳሉ

ፕሬዝደንት ባይደን በመጪው ቅዳሜ የአውስትራሊያ፣ ህንድና ጃፓን መሪዎችን በዋይት ሃውስ ተቀብለው “ኳድ” በሚል የሚታወቀዋን የአራቱን ሃገራት ቡድን ስብሰባ ያስተናግዳሉ። ቡድኑ በተለይም በኢንዶ ፓሲፊክ ቀጠና ባለ ስልታዊ የፀጥታ ትብብር ያተኩራል። ሕዝብ በብዛት የሚገኝበት ቀጠናው ለቻይናም ከኢኮኖሚ እና ከስልት አንጻር ወሳኝ ነው።

የቪኦኤ የዋይት ሃውስ ዘጋቢ አኒታ ፓወል የላከችው ዘገባ ነው።