የሶማልያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረጉ ነው

  • ቪኦኤ ዜና

ፎቶ ፋይል

የሶማልያ ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ዐብዱላሂ ሞሐመድ /ፋርማጆ/ በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በሁለትዮሽና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

የፕሬዚዳንት ሞሐመድ ዐብዱላሂ ጉብኝት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም ለማስፈንና የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር የጀመሩት ዲፕሎማሲያዊ እንቅሰቃሴ አካል ነው ተብሏል።