በፓኪስቲያን “የእስልምናን እምነት ስም አጉድፋለች” በሚል የተከሰሰች በነፃ ተለቀቀች

  • ቪኦኤ ዜና

አስያ ቢቢ

የፓኪስታን ከፍተኛ ፍርድ ቤት “የእስልምናን እምነት ስም አጉድፋለች” በሚል በሀሰት የተከሰሰችውን ክርስትያን ሴት በነፃ መለቀቅን አፅድቋል፤ ለአስርት ዓመት በዘለቀ የፍርድ ሂደት፡፡

የፓኪስታን ከፍተኛ ፍርድ ቤት “የእስልምናን እምነት ስም አጉድፋለች” በሚል በሀሰት የተከሰሰችውን ክርስትያን ሴት በነፃ መለቀቅን አፅድቋል፤ ለአስርት ዓመት በዘለቀ የፍርድ ሂደት፡፡

በአስያ ቢቢ ላይ የተመሰረተው ክስ መሰረት የለውም በማለት ከፍተኛው ፍርድ ቤት ባለፈው ጥቅምት ወር ከበየነ በኋላ ከእስር የተለቀቀች ቢሆንም ከአክራሪ ሙስሊሞች የግድያ ዛቻ ስለተሰነዘረባት ለደኅንነትዋ ሲባል በመንግሥት ጥበቃ ሥር ተደብቃ ቆይታለች።

አሁን ግን ከፓኪስትን ለመውጣት የምትችልበት ዕድል ተፈጥሮላታል። ልጆችዋ በካናዳ ጥገኝነት ተሰጥቷቸዋል፣ ምናልባትም ወዲዚያው ታመራ ይሆናል፡፡