በኦሮሚያ ለአስር ሺሕ የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ተሰጠ

  • እስክንድር ፍሬው
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት አቶ ለማ መገርሳ የተቀመጡ መስፈርቶችን ላሟሉና በፈጸሙት ወንጀል ለተፀፀቱ አስር ሺሕ የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረጉ።

በኦሮሚያ ክልል የተደረገውን ይቅርታ “ገንቢ” ሲሉ የገለፁት የመድረክ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በሀገሪቱ ያለውን ሁኔታ ለማረጋጋት ግን የፖለቲካ መሪዎቻችን አባሎቻችንና በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ የታሰሩ ሌሎችም መፈታት አለባቸው ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ በበኩላቸው በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት የታሰረ ሰው የለም ብለዋል። የተደረገው ይቅርታም የክልሉ ፕሬዚዳንት በመደበኛነት የሚያደርጉት እንጂ ከምንም ወቅታዊ ሁኔታ ጋር የተገናኘ አይደለም ብለዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በኦሮሚያ ለአስር ሺሕ የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ተሰጠ