በኦሮሚያ ክልል በርካታ ዞኖች በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች በወባ ተይዘዋል

ፎቶ ፋይል፦ የወባ ትንኝ

በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ በርካታ ዞኖች፣ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸውን፣ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

በከፍተኛ ደረጃ ከተጠቁት ዞኖች አንዱ በኾነው በምዕራብ ወለጋ ዞን ብቻ፣ ባለፉት ዐሥር ወራት ውስጥ፣ ከ500ሺሕ በላይ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን፣ የዞኑ የጤና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መስፍን ጣሰው ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።

Your browser doesn’t support HTML5

በኦሮሚያ ክልል በርካታ ዞኖች በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች በወባ ተይዘዋል

በዚኹ ዞን የቆንዳላ ወረዳ ነዋሪዎች ደግሞ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ በወባ የሞቱ ሕፃናት መኖራቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በመድኃኒት አቅርቦት ላይ እየሠራ መኾኑን፣ የኦሮሚያ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ገልጿል።