በቦረናና በጉጂ ዞኖች አምስት ሰዎች ከሶማሌ ክልል በመጡ ልዩ ፖሊስ ተገደሉ ተባለ

ሶማሌ ክልል የመጡ የልዩ ፖሊስ ኃይሎች በቦረናና በጉጂ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች ውስጥ ገብተው ባለፉት አራት ቀናት ውስጥ የአምስት ሰዎችን ሕይወት ማጥፋታቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

የቦረናና የጉጂ ዞን ኗሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ አፋን ኦሮሞ ዝግጅት ክፍል እንደገለፁት የተለየ የወታደር ልብስ የለበሱና ከፍተኛ የጦር መሣሪያ የታጠቁ ኃይሎች ወደ ክልላቸው በመግባት የአርብቶ አደሮችን ከብቶች በመውሰድ የቀበሌ ታጣቂዎችን ጨምሮ ግለሠቦችን በማፈን ወደ ክልላቸው ወደ ጎዴ ዞን ወስደዋቸዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በቦረናና በጉጂ ዞኖች አምስት ሰዎች ከሶማሌ ክልል በመጡ ለዩ ፖሊስ ተገደሉ ተባለ