በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሆሮ ቡሉቅ ወረዳ እና በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሆሮ ቡሉቅ ወረዳ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች የኦሮሞ ነፃነት ሸማቂዎችን ከመደገፍ ጋር በተያያዘ ሁለት ወጣቶችንና አንድ መምህር ገደሉ ሲሉ ከቤተሰብ መካከል የቅርብ ዘመድ ነኝ ያሉ ግለሰብ ገለፁ።

የወረዳው ፀጥታና አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ ግለሰቦቹ ስለመገደላቸው ለፅህፈት ቤታቸው ያሳወቀ ባለመኖሩ ምንም አይነት ምርመራ አለመደረጉን አስታውቋል።

በተመሳሳይ ሁኔታ በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳም አንድ ግለሰብ በፀጥታ ሀይሎች ከተያዘ በኋላ ተገድሎ መገኘቱን አንድ የዐይን እማኝ ገልጿል።

የደራ ወረዳ ፀጥታና አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ ይህ ተገደለ የተባለው ግለስብ በወረዳችንም አልታሰረም፤ በወረዳችን የተገደለ ሰውም የለም ብለዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሆሮ ቡሉቅ ወረዳ እና በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ