በ22ቱ ፓርቲዎች ክርክርና ድርድር ላይ መገናኛ ብዙኃን እንዲዘግቡ ተፈቀደ

  • መለስካቸው አምሃ

አቶ ሽፈራው ሽጉጤ

ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ቀደም በለው በሰየሙትና በተወካዮች ምክር ቤት ባለሞያዎች አማካኝነት በቀረበላቸው የክርክር እና የድርድር የአሰራር ረቂቅ ደንብ ላይ ለመወያየት ሌላ ቀጠሮ ተለዋወጡ፡፡

ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ቀደም በለው በሰየሙትና በተወካዮች ምክር ቤት ባለሞያዎች አማካኝነት በቀረበላቸው የክርክር እና የድርድር የአሰራር ረቂቅ ደንብ ላይ ለመወያየት ሌላ ቀጠሮ ተለዋወጡ፡፡ መገናኛ ብዙሃን ያለ ልዩነት በውይይቱ ገብተው እንዲዘግቡ ፓርቲዎቹ ተስማሙ፡፡

በስፍራው ለነበሩ ጋዜጠኞች አዳራሹ ክፍት ሲደረግ ከመድረኩ መሪ እንደተነገረው ከሆነ የዕለቱ አጀንዳ አንድ ብቻ ነበር፡፡

አጀንዳው የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክርና ድርድር የአሰራር ረቂቅ ደንብ ላይ መነጋገር የሚል እንደሆነም በፓርቲዎቹ ስምምነት መድረኩን ይመሩት የነበሩትና የኢሕአዴግ ፅ/ቤት ምክር ቤት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለጉባዔው አስታውሰዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በ22ቱ ፓርቲዎች ክርክርና ድርድር ላይ መገናኛ ብዙኃን እንዲዘግቡ ተፈቀደ