አዋጆች በደቡብ ኦሞ በትክክል እንደማይተገበሩ የኦሕዴኅ መሪ ተናገሩ

  • እስክንድር ፍሬው

የደቡብ ኢትዮጵያ ብብሕ ክልል

“በሀገሪቱ የሚወጡ አዋጆች ከማዕከል ርቆ በሚገኘው ወገናችን በትክክል አይተገበርም” ሲሉ የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት ሊቀ መንበር ተናግረዋል።

እስከ ትላንት፣ ማክሰኞ፣ ኅዳር 6/2016 ዓ.ም. ድረስ ምክትላቸውን ጨምሮ አራት የፓርቲው አመራር አባላት ጂንካ ከተማ ውስጥ መታሠራቸውን የፓርቲው ሊቀ መንበር አቶ ግርማ በቀለ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል፡፡

ፀረ-ሽብር አዋጁ በወጣበት ወቅት የፓርቲያቸው የአመራር አባላት ለሁለት ሣምንታት ታስረው እንደነበር የገለፁት አቶ በቀለ እስሩ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል።

ደቡብ ኦሞ ዞን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት ይፋ በተደረገው ተጠርጣሪዎች የተያዙባቸው ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም።

እስክንድር ፍሬው ዝርዝሩ አለው።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

አዋጆች በደቡብ ኦሞ በትክክል እንደማይተገበሩ የኦሕዴኅ መሪ ተናገሩ