በዲሞክራሲያዊ አሰራር አንዱ የሌላውን ሀሳብ እንዲያከብር ተጠየቀ

በአዲስ አበባ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራር የአቀባበል ሥነ ስርዓት ተከትሎ፣ የድርጅቱን ባንዲራ “እስቅላለሁ፣ አትሰቅልም” የሚል አምባጓሮ ላይ የተፈጠረ ግጭት ዛሬም ለሦስተኛ ቀን ቀጥሏል፡፡

በአዲስ አበባ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራር የአቀባበል ሥነ ስርዓት ተከትሎ፣ የድርጅቱን ባንዲራ “እስቅላለሁ፣ አትሰቅልም” የሚል አምባጓሮ ላይ የተፈጠረ ግጭት ዛሬም ለሦስተኛ ቀን ቀጥሏል፡፡

ችግሩን ለማርገብና ጉዳዩን በውይይትና በመቻቻል ለመፍታት የአዲስ አበባ ወጣቶች ፌዴሬሽንና የኦነግ አቀባበል ሥነ ሥርዓት ኮሚቴ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸው በሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ አሰራር አንዱ የሌላውን አስተሳሰብ በማክበር የጋራ ጉዳያችን ላይ እናተኩር ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

በዲሞክራሲያዊ አሰራር አንዱ የሌላውን ሀሳብ እንዲያከብር ተጠየቀ