"ሀገራዊ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት ብሄራዊ መግባባት መፍጠር ይገባል" - ፓርቲዎች

ሀዋሳ

በኢትዮጵያ እየተቃረበ ያለው አገራዊ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት ሀገሪቱ ገብታበታለች ካሉት የፖለቲካ ቅርቃር ለማውጣት ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ ከማካሄድ በፊት ብሄራዊ መግባባት መፍጠር እንደሚገባ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ኦፌኮና የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ተናግረዋል።

ፕሮፌሰር መረራ በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ በሚገኙ የፖለቲካ ኃይሎች መካከል በስፋት እየታየ ነው ያሉት የፖለቲካ ፍጥጫ፥ የገዥው ፓርቲ መከፋፈል የብልጣብልጦች ጨዋታ ያሉት በሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚፈልጉ አካላት ጥረት የፖለቲካ ቅርቃር ማሳያ ናቸው።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

"ሀገራዊ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት ብሄራዊ መግባባት መፍጠር ይገባል" - ፓርቲዎች