በሐብሩ ወረዳ የተኩስ ልውውጥ ባልታጠቁ ነዋሪዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱ ነዋሪዎች አስታወቁ

በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ ውርጌሳ ከተማ አካባቢ

በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ ውርጌሳ ከተማ አካባቢ፣ ባለፈው ሳምንት ኀሙስ፣ በመከላከያ ኀይል እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ፣ ባልታጠቁ ሰዎች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱን ነዋሪዎች አስታወቁ።

በከተማው የጸጥታ ችግር እንደነበርና የተጎዱም ሰዎች መኖራቸውን የጠቀሰው የሐብሩ ወረዳ አስተዳደር፣ አኀዛዊ መረጃ ለመስጠት ግን በምርመራ ላይ መኾኑን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በሐብሩ ወረዳ የተኩስ ልውውጥ ባልታጠቁ ነዋሪዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱ ነዋሪዎች አስታወቁ

ከውርጌሳ ከተማ በተጨማሪ፣ በተለያዩ የሐብሩ ወረዳ አቅራቢያዎችም የጸጥታ ችግር እንደሚስተዋል የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ሑሴን መሐመድ፣ በሕዝቡ ዕለታዊ ኑሮ ላይ ጫና መፍጠሩን አመልክተዋል።