የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላዲሚር ፑቲን የሰሜን ኮርያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን መጀመርያ የማስተማመኛ ዋስትና ካገኙ የኑክሌር መሳርያን ሊያስወግዱ ይችላሉ የሚል ዕምነት እንዳላቸው ገልፀዋል።
ዋሺንግተን ዲሲ —
ፑቲን ይህን ያሉት ቭላዲቫስቶክ በተባለቸው የሩስያ የሩቅ ምስራቅ ከተማ ላይ ከሰሜን ኮርያው መሪ ጋር ለመጀመርያ ጊዜ ከተነጋገሩ በኋላ ነው።
ሁለቱ መሪዎች ከተነጋገሩ በኋላ ባደረጉት ጋዜጣዊ ጉባኤ ኑክሌር መስርያን የማስወገዱ ሂደት ደረጃ በደርጃ መሆን እንዳለበት ፑቲን ሲያስረዱ ዩናይትድ ስቴትስና ሰሜን ኮርያ የመተማመን መንፈስ ለመገንባት ሲሉ የቀስ በቀ እርምጃ መውሰድ ይኖርባቸዋል በማለት መክረዋል።