በሰሜን ኮሪያ መንግሥት ላይ ይፋ የተደረገ ሪፖርት

  • ሰሎሞን ክፍሌ

ፎቶ ፋይል

የሰሜን ኮሪያ መንግሥት ላለፉት አሥርት ዓመታት ካዝናውን ለመሙላት ሲተማመን የቆየው፣ በሕገወጥ ንግድ በሚያገኘው ገንዘብ ላይ ነበር።

የሰሜን ኮሪያ መንግሥት ላለፉት አሥርት ዓመታት ካዝናውን ለመሙላት ሲተማመን የቆየው፣ በሕገወጥ ንግድ በሚያገኘው ገንዘብ ላይ ነበር።

አዲስ ይፋ የተደረገ ሪፖርት ግን፣ ፒዮንግያንግ ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፖብሊክን፣ አንጎላን፣ ሞዛምቢክንና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ፣ ከአፍሪካ ሃገሮች ጋር በዱር አራዊቶች ላይ የምታካሂደው ሕገወጥ ንግድ ባለፉት ሦስት ዓመታት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ያመለክታል።

/ግሎባል ኢንሸቲቩ አጌነስት ትራንዝሺናል ኦርጋናይዝድ ክራይምስ/ የተባለውና በሃገሮች መካከል ተቀነባብሮ የሚካሄደውን ወንጀል የሚቆጣጠረው ዓለምቀፍ ድርጅት አዲስ ያወጣው ሪፖርት ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ የአህጉሪቱ ብርቅዬ የአውራሪስና ዝሆን ዝርያዎች ጨርሶ ይጠፋሉ ሲል አስጠንቅቋል።

Your browser doesn’t support HTML5

በሰሜን ኮሪያ መንግሥት ላይ ይፋ የተደረገ ሪፖርት