ሰሜን ኢትዮጵያ - አገልግሎቶችና እርዳታ

በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና

ሰሜናዊ አካባቢዎች የተለያዩ አገልግሎቶችን የማስጀመርና እርዳታ የማከፋፈል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል።

የጥገና ሥራዎች በታቀደው ጊዜ መጠናቀቃቸውንና ከአሥር በላይ ከተሞችና በዙሪያቸው የሚገኙ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘታቸውን የድርጅቱ የወልዲያ ቢሮ ገልጿል።

በሌላ በኩል በጦርነቱ ምክንያት ለችግርና ለጉዳት ለተጋለጡ ከ395 ሺህ በላይ ሰዎች እርዳታ መድረሱን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ አገልግሎት ዛሬ አስታውቋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን ዘገባ ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ሰሜን ኢትዮጵያ - አገልግሎቶችና እርዳታ