በናይጄሪያ የካዱና ግዛት የቦምብ ጥቃት በጥልቀት እንዲመረመር ፕሬዚዳንቱ አዘዙ

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

በናይጄሪያ የካዱና ግዛት የቦምብ ጥቃት በጥልቀት እንዲመረመር ፕሬዚዳንቱ አዘዙ

ባለፈው እሑድ፣ በሰሜናዊ ካዱና ግዛት በሚገኝ መንደር፣ በሙስሊም ምእመናን ላይ ስለደረሰው የቦምብ ጥቃት፣ የጸጥታ ተቋማት እና የመንግሥት ባለሥልጣናት ጥልቅ ምርመራ እንዲያደርጉ፣ የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኒፉ አዘዙ።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ በቦምብ ጥቃቱ ቢያንስ 120 ሰዎች እንደሞቱ፣ የመስክ ሠራተኞችንና የአካባቢው ነዋሪዎችን ዘገባ ጠቅሶ አስታውቋል፡፡

ቲሞቲ ኦቢዙ ከናይጄሪያ መዲና አቡጃ ተከዩን ዘገባ ልከዋል ደረጀ ደስታ ወደ ዐማርኛ መልሷል፡፡