የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ያላት ሕገ መንግሥታዊ ጥቅምና አሁን ያለበት ደረጃና ወደፊት በሚል የመመረቂያ ትናት የሠሩት የሕግ ባለሞያ አስተያየት ሰተዋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለውን ልዩ ጥቅም የሚያስጠብቅ ረቂቅ ዐዋጅ የሚንስትሮች ም/ቤት አፅድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቶታል። ዛሬ ሰኔ 22/2009 ዓ.ም የተሰበሰበው ምክር ቤቱ ረቂቁን ለሕግና አስተዳደር ጉዳዮችና ለከተማ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል። ምክር ቤቱ ለእረፍት ሊዘጋ አንድ ሳምንት ብቻ የቀረው በመሆኑ ውይይት ሳይደረግበት በቀሪው ጊዜ እንዲፀድቅ እንደማይደረግ አፈ ጉባኤው አባዱላ ገመዳ ለአባላቱ ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5