ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምርጫ ጊዜያዊ ሰሌዳ ወጣ

ሶሊያና ሽመልስ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 6ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ታህሳስ 21/2014 ዓ.ም ለማካሔድ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "ጊዜያዊ" ያለውን የጊዜ ሰሌዳ አወጣ።

የጊዜ ሰሌዳው የወጣው ከክልሉ የጸጥታ ተቋማት እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመነጋገር መሆኑን የቦርዱ የኮሙኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል ቦርዱ ምርጫውን ለማካሔድ ያቀደው፣ የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ መሻሻል በማሳየቱ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡

የክልሉን ሠላም በማረጋገጥ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርጫውን በማካሄድ አዲስ መንግሥት ለመመስረት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጠቁመዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምርጫ ጊዜያዊ ሰሌዳ ወጣ