የወላይታ ዞን ውሳኔ ሕዝብ በድጋሚ ሊካሄድ ነው

  • መለስካቸው አምሃ

Your browser doesn’t support HTML5

የወላይታ ዞን ውሳኔ ሕዝብ በድጋሚ ሊካሄድ ነው

የወላይታ ዞን ሕዝበ ውሳኔ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የመራጮች ምዝገባ እና ድምፅ የመስጠቱ ሂደትም በአንደ ቀን እንደሚከናወን ቦርዱ ይፋ አድርጓል፡፡ በወላይታ ዞን የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውሳኔ ሕዝቡ መካሔዱን ተቃውመዋል፡፡

ምርጫ ቦርድ ባለፈው ጥር ወር ተካሂዶ በነበረው ውሳኔ ሕዝብ፣ በወላይታ ዞን የተከናወነው የተጭበረበረ መኾኑን ይፋ አድርጎ ውሳኔ ሕዝቡ በድጋሚ እንደሚካሔድ መግለፁ ይታወሳል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡