በሞያሌ የፀጥታ ችግር የ13 ሰዎች ህይወት አለፈ

ፎቶ ፋይል

ትላንት በሞያሌ በተከሰተው የፀጥታ ችግር 13 ሰዎች መሞታቸውንና በርካቶች ደግሞ መቁሰላቸውን የኦሮሚያ ክልል አስታወቀ።

ትላንት በሞያሌ በተከሰተው የፀጥታ ችግር 13 ሰዎች መሞታቸውንና በርካቶች ደግሞ መቁሰላቸውን የኦሮሚያ ክልል አስታወቀ። ግድያውን የፈጸሙት ከክልል 5 የመጡ ታጣቂዎች እንዲሁም በከተማዋ ሠፍሮ ያለ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል መሆናቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የሞያሌ ከተማ ከንቲባ ስለ ግድያው ተጠይቀው በሞያሌ ሠፍሮ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል በግድያው እጁ እንዳለበት ተናግረዋል። በሞያሌ ዛሬም ተኩሱ ቀጥሏል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

በሞያሌ የፀጥታ ችግር የ13 ሰዎች ህይወት አለፈ