በሞሱል በተመረዘ ምግብ ሰዎች መታመማቸውና መሞታቸው ተገለፀ

  • ቪኦኤ ዜና
በጦርነት በተጠመደችው በኢራቅዋ ሞሱል ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ በተመረዘ ምግብ ምክንያት ሰባት መቶ ሃምሳ ሁለት ሰዎች መታመማቸው ተገለጠ።

በጦርነት በተጠመደችው በኢራቅዋ ሞሱል ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ በተመረዘ ምግብ ምክንያት ሰባት መቶ ሃምሳ ሁለት ሰዎች መታመማቸው ተገለጠ።

ሶስት መቶ አሥራ ሁለት ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። ቢያንስ ሁለት ሰዎች ሞተዋል።

ሊሳ ሽላይን የዓለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት /IOM/ ፅሕፈት ቤት ከሚገኝበት ከጄኔቫ ለቪኦኤ ያጠናቀረችውን ዘገባ ቆንጂት ታየ ታቀርበዋለች።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በሞስል በተመረዘ ምግብ ሰዎች መታመማቸውና መሞታቸው ተገለፀ