ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ፣ እአአ ከ1992 ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ በከፍተኛ ደረጃ የተሰራጨ 33 አዳዲስ የኩፍኝ ወረርሽኝ ባለፈው ሳምንት ብቻ መገኘቱ ተገለፀ።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የአዲሱን ስርጭት ጠቅላላ ድምር 107 እንዳደረሰው፣ የጤና አገልግሎት ባለሥልጣኖች አመልክተዋል።
አስከፊ የተባለው ከፍተኛ ስርጭት፣ ከሃያ-አምስት ዓመት በፊት የነበረውና 2,126 ህሙማን የተመዘገቡበት መሆኑ ይታወሳል።
ወረርሽኙ በ33 ሴቴቶች መዛመቱ የተገለፀ ሲሆን በተለይ በካሊፎርኒያ፣ በኒው-ዮርክ፣ በፔንሲልቬንያና በዋቪንግተን ስቴት ስርጭቱ እንደቀጠለ ተገልጧል።