ፍልሰት ወደ አረብ ሀገራት

Your browser doesn’t support HTML5

በደቡብ ወሎ በኩል ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ሃገሮች ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ሊሸጋገሩ የነበሩ ቁጥራቸው ወደ አንድ ሺህ የሚሆን ሰዎች ተይዘው ወደ የተነሱባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ መደረጉን የዞኑ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታውቋል። ወደ አረብ ሃገሮች ለመሸጋገር ሲሞክሩ የተያዙት ከኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ ወጣቶች መሆናቸውን መምሪያው ያለፉ አምስት ወራት እንቅስቃሴውን አጣቅሶ በሰጠው መግለጫ ላይ አመልክቷል።