የትግራይ ተፈናቃዮች ከሰኔ 30 ቀን በፊት ወደቀዬአቸው ለመመለስ በድጋሚ ጠየቁ

ፎቶ ፋይል፦ መቀሌ

በትግራይ ክልል የተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች፣ ወደ ቀዬአቸው ለመመለስ የጠየቁበትን ሰላማዊ ሰልፍ፣ ትላንት እሑድ አካሒደዋል፡፡

በመቐለ ከተማ ሰልፍ የወጡ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች፣ መንግሥት ቃል በገባው መሠረት፣ ከሰኔ 30 ቀን በፊት ወደ ቀዬአችን ይመልሰን፤ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ተፈናቃዮች ከሰኔ 30 ቀን በፊት ወደቀዬአቸው ለመመለስ በድጋሚ ጠየቁ

በሰልፉ ላይ፣ ተፈናቃዮች በተደጋጋሚ ሰልፍ መውጣታቸውን ያወሱት፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፣ “የአሁኑ ሰልፍ የመጨረሻ ይኾናል፤” ብለዋል፡፡

የተፈናቃዮቹን አመላለስ ያለጸጥታዊ ችግር ለመፈጸም እንደሚሠራ ፕሬዚዳንቱ አመልክተዋል፡፡