"ብሄር እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን"

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ተግባቦት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር ሙላቱ አለማየሁ

በኢትዮጵያ ብሄርን ወይም ክልሎችን መሰረት አድርገው የተቋቋሙ መገናኛ ብዙሃን በአክራሪ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ የተተበተቡ እና የሞያውን ስነምግባር ወደጎን የተው መሆናቸውን በጥናት ማረጋገጣቸውን ምሁራን ተናገሩ።

በምህፃሩ «ኢናሚሳ» የተሰኘ የኢትዮጵያ ብሄራዊ መገናኛ ብዙሃን ድጋፍ ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት አውደ ርዕይ ላይ ጥናቱን ያቀረቡት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር እና በኢዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ተግባቦት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር ሙላቱ አለማየሁ መገናኛ ብዙሃን ከዚህ ችግር ካልወጡ በሃገሪቱ ህልውና ላይ የሚያስከትሉት አደጋ ከፍተኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

"ብሄር እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን"