በአማራ ክልል የአምበጣ መንጋ በሰብል ላይ ጉዳት አደረሰ

የአምበጣ መንጋ

የአምበጣ መንጋ በምስራቃዊ የአማራ አካባቢዎች በሰብልና በሌሎች እጽዋት ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው፡፡

በተለይ ከአፋር በሚያጎራብቱ ወረዳዎች ላይ ጉዳቱ የከፋ ነው ተብሏል፡፡ በደቡብ ወሎ ወረባቦ አካባቢ

የሚገኙ አርሶ አደሮች ጥፋቱ ህልውናችንን ይፈታተነዋል ብለዋል፡፡

በወረባቦ ወረዳ ቦከክሳና ገታሪ አካባቢ የሚኖሩት አርሶ አደሮች ከእሸቱ እንቋደሳለን በምርቱ ቀለባችንን እንችላለን ያሉበት የማሽላ ሰብል ሙሉ በሙሉ በአምበጣ መንጋው ወድሞባቸዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራ ክልል የአምበጣ መንጋ በሰብል ላይ ጉዳት አደረሰ