በላሊበላ ከተማ ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

ፎቶ ፋይል፦ ላሊበላ ከተማ

ፎቶ ፋይል፦ ላሊበላ ከተማ

በአማራ ክልል በግጭት ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች ወደ ሰላም እንዲመጡ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ በሰሜን ወሎ ዞን ላሊበላ ከተማ ተካሂደ፡፡

ሰልፈኞቹ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የቱሪዝም እንቅስቃሴው ተስተጓጉሏል፤ የከፋ ድህነት እየተስተዋለ ነው ብለዋል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በላሊበላ ከተማ ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

ሰልፉ በመንግሥት ትእዛዝና አስገዳጅነት እንጅ በሕዝብ ፍላጎት የተዘጋጀ አይደለም ሲሉ ለአሜሪካ ድምጽ የተናገሩም አሉ፡፡

የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ሰልፉን ከአጎራባች ወረዳዎች ጋራ በመተባበር ማዘጋጀቱን አስታውሶ በፈቃደኘነት እንጅ በአስገዳጅ ትእዛዝ የተሳተፈ የለም ሲሉ ትችቱን አስተባብለዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።