በኮንሶ በግጭት ሰባት ሰዎች ሞቱ

ፎቶ ፋይል፦ ኮንሶ

በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን የቀድሞ የሰገን አከባቢ ህዝቦች ዞን ዋና ከተማ ሰገን በተቀሰቀሰ ግጭት ሰባት ሰዎች መገደላቸውን የዓይን እማኞች መሆናቸውን የገለፁ ተናገሩ።

የክልሉ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ በግጭቱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር በወታደራዊ የዕዝ ትዕዛዝ እንደሚገለፅ ጠቁመው ከዘጠኝ ሺህ በላይ ዜጎች ግን ከጉዳት ሸሽተው መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።

ግጭቱ አገር የማፍረስ ሴራ አካል ነው ያሉት ኃላፊው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ግጭቱን እየመሩ የነበሩ 69 ዘጠኝ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በኮንሶ በግጭት ሰባት ሰዎች ሞቱ