ሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞኖችን የሚያጎራብቱ አካባቢዎች እየተረጋጉ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞኖችን የሚያጎራብቱ አካባቢዎች እየተረጋጉ ነው

በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞኖችን በሚያጎራብቱ አካባቢዎች የተቀሰቀሰው ግጭት እየተረጋጋ መሆኑ ተገለፀ፡፡

አንድ ሳምንት የዘለቀውና ለሰዎች ሞት፣ አካል ጉዳት፣ መፈናቀልና ንብረት ውድመት ምክንያት የሆነው ግጭት እየተረጋጋ መምጣቱን ከሁለቱም ዞኖች የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ነገር ግን በአካባቢዎቹ በተደጋጋሚ የሚቀሰቀሱት ግጭቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲገኙና በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ሁሉም የበኩሉን እንዲያበረክት አስተዳዳሪዎቹ ጠይቀዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ያገኛሉ፡፡