በ7መቶ ፍልሰተኞች ሕይወት መጥፋት ተጠያቂው ቱኒዚያዊ መርከበኛ 18 ዓመት ተፈረደበት

  • VOA

ሙሐመድ አሊ ማሌክ

የሜድትሬኒያንን ባህር በማቋረጥ ወደ አውሮፓ ለመጓዝ ባደረጉት ሙከራ ከ7መቶ በላይ ፍልሰተኞች ህልፈት ተጠያቂ ነው የተባለ ቱኒዚያዊ መርከበኛ የ18 ዓመት እስራት ተፈረደበት፡፡

የኢጣልያ ፍርድ ቤት ነው ሜዲትሬንያን ባሕር ውስጥ ሕወታቸውን ላጡ በመቶዎች ለሚቆጠሩ ፍልሰተኞች ሞት ተጠያቂ ባለው ቱኒዝያዊ የመርከብ አዛዥ ላይ የ18 ዓመት እስራት የበየነው።

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ የተፈፀመ ከፍተኛው እልቂት የተባለው ይህ አደጋ የደረሰው፣ እ.አ.አ በሚያዝያ ወር 2015 ዓ.ም ወደ አውሮፓ በመሰደድ ላይ የነበሩ ቢያንስ 7መቶ የሚሆኑ ፍልሰተኞች ሜዲትሬንያን ባሕር ውስጥ በመግባታቸው ነው።

ችሎታ ሳይኖረው የመርከብ አዛዥ የነበረው ሙሐመድ አሊ ማሌክ በህገ-ወጥ አጓጓዥነትና በነፍስ ግድያም ተጠያቂ ስለሆነ ነው የ18 ዓመቱ እስራት የተበየነበት።